በወጣት ማዕከላት የሚካሄደው ሪፎርም የሚነሱ ችግ...

image description
- ውስጥ ወጣቶች    0

በወጣት ማዕከላት የሚካሄደው ሪፎርም የሚነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያስችል ተገለጸ

በወጣት ማዕከላት የሚካሄደው ሪፎርም የሚነሱ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እንደሚያስችል ተገለጸ

ሕዳር 19 ቀን 2017 ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት በዘርፍ በክፍለ ከተማ እና በወረዳ ባለፉት አራት ወራት የተከናወኑ ተግባራትን ገመገመ

ለዝግጅቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መክብብ ወልደሃና ወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት ለወጣቱ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸው የወጣቶችን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል

የወጣቶች ማብቃት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ንብረት ይሁኔ በበኩላቸው ባለፉት አራት ወራት በዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት ላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት የተሰጣቸውን ተልእኮ በብቃት ለፈጸም ያደረጉት እንቅስቃሴ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል

በመድረኩ የማዕከላቱን አገልግሎት አሰጣጥ የተመዘገቡ ጥንካሬ እና የታዩ ክፍተቶች ሰፊ ዉዉይት ተደርጎ መፍትሄ አቅጣጫዎች ተቀምጧል

አቶ መክብብ ወልደሃና በሰጡት የስራ አቅጣጫ የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በወጣት ስብዕና ማዕከላት የሪፎርም ስራ የግንዛቤ ንቅናቄ ስራዎች ላይ በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተው ማዕከላትን በገቢ ምንጭ ለማጠናከር ጣልቃ ገብነት እና የሰው ኃይል ችግርን ለመቅረፍ እንደሚሰራ ገልጸዋል

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014

👍👍👍ትዊተር

https://twitter.com/compose/tweet

👍👍👍ቲክቶክ

https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/

👍👍👍ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/

👍👍👍 ኢሜል

addissport2013@gmail.com

+12

ሁሉም የስሜት መግለጫዎች

109Seyoum Wolde፤ Mes Ethio እና 107 ሌሎች


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.