
መቻል የወንዶች ሲቲ ካፕ የእጅ ኳስ ውድድር ሻምፒዮና ሆነ
መቻል የወንዶች ሲቲ ካፕ የእጅ ኳስ ውድድር ሻምፒዮና ሆነ
ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ያዘጋጀው የአዲስ አበባ ሲቲ ካፕ የወንዶች የእጅ ኳስ ውድድር በመቻል ስፖርት ክለብ አሸናፊነት ተጠናቀቀ ።
መቻል ከፌደሬል ማረም ቤቶች ለዋንጫ ያደረጉት ጠንካራ ፉክክር በመቻል አሸናፊነት ተጠናቋል
መቻል ስፖርት ክለብ ውድድሩን በበላይነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዴልያና የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን ፌደራል ማረሚያ እጅ ኴስ ቡድን የብር አዲስ አበባ ወጣት በቡድን የነሀስ ሜዴልያ ተሸላሚ ሆነዋል
ስፓርቱን ለማጠናከር እና በህበረተስቡ ዘንድ መነቃቃት ለመፍጠር ጠንክሮ መስራት ያስፋጋል ያሉት የፌድሬሽኑ ፕሬዘዳንት አቶ ሳሙኤል ንጉሱ የእጅ ኳስ ስፖርት ዕድገት ባለሃብቱ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል
በአራት ኪሎ ስፖርት ትምህርትና ስልጠና ማዕከል ከህዳር ቀን እስከ 12 2017 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው የሲቲ ካፕ እጅ ኳስ ሻምፒዮና ውድድር ላይ ስድስት ክለቦች መሳተፋቸውን የፌዴሬሽኑ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ተክለማርያም ሊጋባ ነግረውናል
ውድድሩን በስፓርታዊ ጨዋነት እንዲጠናቀቅ ያደረጉ ክለቦችን እና አሰልጣኞችን ያመሰግነቱት አቶ ተክለማርያም ስፖርቱን በከተማ ደረጃ ለማስፋፋትና ተተኪ ስፖርተኞችን በጥራትና በብዛት ለማፍራት ሁሉም ክፍለ ከተሞች ክለብ እንዲይዙ ጠይቀዋል
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን
ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219
ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014
ትዊተር
https://twitter.com/compose/tweet
ቲክቶክ
https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/
ኢንስታግራም
https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/
ኢሜል
addissport2013@gmail.co
ሁሉም የስሜት መግለጫዎች
69Dawit Dave፤ Gossaye Alemayehu እና 67 ሌሎች
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.