
የማይድሴት ስልጠናዎች ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያላቸውን አመለካከት እና አስተሳሰብ የመለወጥ ከፍተኛ አቅም አላቸው። አቶ በላይ ደጀን
የማይድሴት ስልጠናዎች ወጣቶች በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያላቸውን አመለካከት እና አስተሳሰብ የመለወጥ ከፍተኛ አቅም አላቸው። አቶ በላይ ደጀን
ታህሳስ 09 ቀን 2017ዓ.ም ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ በመዲናዋ በሚገኙ በ11 ዱም ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ ወጣቶች በስራ ስድል ፈጠራ ላይ ያተኮረ የማይድ ሴት ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
የማይድ ሴት ስልጠናው የወጣቶችን በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያላቸውን የአመለካከት እና አስተሳሰብ የመለወጥ አቅም እንዳለው አቶ በላይ ደጀን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ሀላፊ አቶ በላይ ደጀን ተናግረዋል።
የከተማው ወጣቶች ከስራ ፈላጊነት ተላቀው ስራ ፈጣሪ እየሆኑ መምጣታቸውን የተናገሩት አቶ በላይ በዚህም በርካታ ወጣቶች የራሳቸውን እና የቤተሰባቸውን ህይወት መቀየር እንደቻሉ ገልፀዋል።
ባላቸው ጉልበት፣ እውቀት፣ ልምድ እና መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ወጣቶች ሰርተን ለፍተን ጥረን መቀየር እንችላለን የሚል አስተሳሰብ እንዲኖራቸው የማይድ ሴት ስልጠናዋች እንደሚጠቅሙ የተናገሩት የቢሮው ሀላፊው እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
ቢሮው ባለፉት 4 ወራት ለወጣቶች በስራ እድል ፈጠራ ላይ በሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከ37ሺህ ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር ችሏል።
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን
ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219
ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014
ትዊተር
https://twitter.com/compose/tweet
ቲክቶክ
https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/
ኢንስታግራም
https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/
ኢሜል
addissport2013@gmail.com
ሁሉም የስሜት መግለጫዎች
24አዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ Addis Ababa Youth and Sport Bureau . እና 23 ሌሎች
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.