
የባህል ስፖርት ውድድር እና ፌስቲቫል ለሚሳተፈው የስፓርት ልዑካን ሽኝት ተደረገለት
የባህል ስፖርት ውድድር እና ፌስቲቫል ለሚሳተፈው የስፓርት ልዑካን ሽኝት ተደረገለት
የካቲት 26 ቀን 2017 ዓ/ም ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሆሳዕና ከተማ ለሚካሄደው 22ኛው የባህል ስፖርት ውድድር እና 18ኛው ስፖርት ፌስቲቫል ለሚሳተፈው የአዲስ አበባ ስፓርት ልዑክ ሽኝት ተደረገለት
የብሔር ብሔረስቦች መኖሪያ የአፍሪካ መዲና የዲፕሎማቶች ማረፊያ አዲስ አበባ ወክለው የሚወዳደሩ የስፓርት ልዑካን ትልቅ አደራ እንዳለባቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን አስገንዝበዋል
በአገር አቀፍ የታዳጊዎች ምዘና ላይ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ያስታወሱት አቶ በላይ የአሸናፊነት ሥነ ልቦና ተላብሳችሁ አዲስ አበባ አንደኛ ማድረግ ይጠበቅባችዋል ብለዋል
ባሕላዊ ስፓርቶች ለዘመናዊ ስፓርቶች መነሻ በመሆናቸው ታሪካዊ እሴቶቻቸውን በመጠበቅ ለተተኪው ትውልድ ማሻገር እንደሚገባ አቶ በላይ ገልጸዋል
በውድድር ከማሸነፍ ባሻገር አዲስ አበባን የሚያስጠራ መልካም ስራ መስራት ከስፓርት ልዑክ እንደሚጠበቅ አቶ በላይ አመላክተዋል
ቢሮው ባህል ስፓርትን ለማሳደግ በታዳጊዎች ላይ በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወሱት ምክትል ቢሮ ኃላፊው አቶ ዳዊት ትርፋ የባህል ስፓርት ውድድር በስኬት ለማጠናቀቅ ተወዳዳሪዎች ከልምምድ ጀምሮ የተሰራውን ስራ ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስበዋል
ባህላዊ ስፖርቶች ወንድማማችነትን እህትማማችትን ለማጎልበት ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው የገለጹት አቶ ዳዊት ባለፉት ዓመታት የተመዘገቡትን የአሸናፊነት ጉዞ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል
ከ150 በላይ የአዲስ አበባ ስፓርት ልዑካን ወደ ስፍራው በማቅናት በአስረ አንድ የስፓርት አይነት እንደሚሳተፉ ተመልክቷል
ባህላዊ ውድድርና ፌስቲቫሉ ባህላዊ ስፖርቶቻችን ለጠንካራ ህብረ ብሄራዊ አንድነታችን በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 7 2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚካሄድ ተመልክቷል
ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ እናመሰግናለን
ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219
ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014
ትዊተር
https://twitter.com/compose/tweet
ቲክቶክ
https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/
ኢንስታግራም
https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/
ኢሜል
addissport2013@gmail.com
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.