#እንኳን_ደስ_አላችሁ_እንኳን_ደስ_አለን!!!...

image description
- ውስጥ ስፖርት    0

#እንኳን_ደስ_አላችሁ_እንኳን_ደስ_አለን!!! ሀገርን በመወከል ሊብያ ቤንጋዚ ዓለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር ላይ የተሳተፈው የአዲስ አበባ ልዑክ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።

#እንኳን_ደስ_አላችሁ_እንኳን_ደስ_አለን!!!

ሀገርን በመወከል ሊብያ ቤንጋዚ ዓለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር ላይ የተሳተፈው የአዲስ አበባ ልዑክ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ።

ነሐሴ 10 ቀን 2017ዓ.ም ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ

ኢትዮጵያን በመወከል በሊቢያ ቤንጋዚ በተዘጋጀው አለም አቀፍ የብስክሌት ውድድር ላይ የተሳተፈው የአዲስ አበባ ከተማ የብስክሌት ልዑክ አጠቃላይ አሸናፊ በመሆን ውድድሩን አጠናቆል።

ውድድሩ ከነሐሴ 7 እስከ 9 የተካሄደ ሲሆን በቡድን በተካሄደ ውድድር ኢትዮጵያ አንደኛ ሆና ስታጠናቅቅ ሞሮኮና ግብፅ ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

በተመሳሳይ በግል ኢትዮጵያዊ አንደኛ እና ስስተኛ ደረጃን በመያዝ ስታጠናቅቅ ሞሮኮ ሁለተኛ በመሆን ውድድሮን አጠናቃለች።

ሀገርን ወክሎ የተሳተፈው እና አጠቃላይ አሸናፊ የሆነው የአዲስ አበባ የብስክሌት ልዑክ የወርቅ ሜዳልያና የገንዘብ ሽልማት ከአወዳዳሪው አካል እንደተበረከተለት ልዑክ ቡድኑን የመሩት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ም/ቢሮ ሀላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ ተናግረዋል።

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014

👍👍👍ትዊተር

https://twitter.com/compose/tweet

👍👍👍ቲክቶክ

https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/

👍👍👍ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/

👍👍👍 ኢሜል

addissport2013@gmail.com

 

Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.