በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 35ሺ ዩኒት ደም...

image description
- ውስጥ ወጣቶች    0

በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 35ሺ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ እየተስራ መሆኑ ተገለጸ ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ

በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት 35ሺ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ እየተስራ መሆኑ ተገለጸ

ሐምሌ 6 ቀን 2016 ዓ.ም ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አዳዲስ ደም ለጋሾችን በማካተት 35ሺ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ እየስራ መሆኑን አስታወቀ

የደም ልገሳው ደሜን ለወገኔ በሚል መሪ ቃል በሁሉም ክፍለ ከተሞች እየተካሄደ እንደሚገኝ የገለጹት የወጣቶች ግንዛቤና ንቅናቄ ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጤናዬ ታምሩ ወጣት አደረጃጀቶችን እና በጎ ፈቃደኞችን በማስተባበር ሕይወት የሆነውን ደም በመስጠት ሕይወት ያድኑ የሚለውን ዓለም አቅፋዊ መርህ እየተተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል

ዕቅዱን ሙሉ ለሙሉ ለማሳካት አዳዲስ የደም ለጋሽ በጎ ፈቃደኞችን የማሳተፍ ስራ እየተስራ መሆኑን ያወሱት አቶ ጤናዬ ደም መስጠት ህይወት ማዳን በመሆኑ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ደም እንዲለግስ ጥሪ አቅርበዋል

በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አንዱ የሆነውን ደም የመለገስ በጎ ስራ በንቅናቄ ማስጀመሪያ ወቅት ከፍተኛ አመራሮችን በማካተት መከናወኑን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ በተመረጡ አደባባዮች ከተማ አቀፍ የደም ልገሳ ንቅናቄ እንደሚደረግ ጠቁመዋል

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ጋር የደም ልገሳ ፕሮግራሙን በስፋት እያከናወነ እንደሚገኝ የላከልን መረጃ ያስረዳል

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014

👍👍👍ትዊተር

https://twitter.com/compose/tweet

👍👍👍ቲክቶክ

https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/

👍👍👍ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/

👍👍👍 ኢሜል

addissport2013@gmail.com

 


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.