በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት የተከናወኑ ወ...

image description
- ውስጥ ወጣቶች    0

በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት የተከናወኑ ወጣት ተኮር ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ

በወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት የተከናወኑ ወጣት ተኮር ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ

ጥቅምት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ

አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት የወጣቶች ፍላጎት መሰረት በማድረግ የሚሰጣቸ ወጣት ተኮር ስራዎች አበረታች መሆናቸው ተገለጸ

የወጣቶች የማብቃት ዳይሮክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ንብረት ይሁኔ ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹልን የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት ወጣቶች በፍላጎታቸው የሚሰሩበት የሚሰጡ አገልግሎቶች በመጠቀም ራሳቸውን ካልባሌ ነገር በመጠበቅ በአገር ፍቅር ስሜት በመታነጽ እሴቶቻቸውን የሚያሳድጉበት መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከል ግንባታ በሁሉም ወረዳዎች በማዳረስ አገልግሎት በማዘመንና ደረጃቸውን በማሻሻል ባለፈው ሩብ ዓመት 1,283,341 ወጣቶች በማዕከላቱ በሚሰጡ አገልግሎቶች እንዲጠቀሙ ማድረግ መቻሉን የገለጹት አቶ ለ110 የወጣቶች ስብዕና መገንቢያ ማዕከላትን ማየት ለተሳናቸው ወጣቶች የጃውስ አፕሊኬሽን መጫን መቻሉን ነግረውናል፡፡

የወጣቶች ስብእና መገንቢያ ማእከላት በቴክኖሎጂ ታግዘው ደረጃቸውን የጠበቁ አገልግሎት በመስጠት ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የነገሩን አቶ ንብረት ለአራት የስብዕና መገንቢያ ማዕከላት 20 ኮምፒተሮችን ድጋፍ በማድረግ የአገልግሎት አስጣጣቸውን እንዲያሻሻሉ ማድረግ ተችሏል፡፡

የወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት ዋና ተግዳሮት የሆነውን ጣልቃ ገብነትን ለመፍታት እና ማዕከላቱን ሳቢ እና ማራኪ ለማድረግ የሚሰሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የወጣቶች ማብቃት ዳይሮክቶሬት ያደረሰን መረጃ ያስረዳል፡፡

ታማኝ ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች ለማግኘት የቢሮውን ማኅበራዊ ሚዲያ ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ 👇👇👇እናመሰግናለን

👍👍👍 ፌስ ቡክ ገጽ:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100069054105219

👍👍👍 ቴሌግራም ቻናል: https://t.me/youthsport2014

👍👍👍ትዊተር

https://twitter.com/compose/tweet

👍👍👍ቲክቶክ

https://vm.tiktok.com/ZM2j4H9mE/

👍👍👍ኢንስታግራም

https://www.instagram.com/addis_abeba_youth_and_sport_/

👍👍👍 ኢሜል

addissport2013@gmail.com

May be an image of 2 people and text

All reactions:

92አዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ Addis Ababa Youth and Sport Bureau . and 91 others


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.