ክስተቶች

ውስጥ ስፖርት

image description
የመጀመሪያ ቀን icon
የመጨረሻ ቀን icon
አካባቢ አዲስ አበባ, Abebe Bikala Stadium

value="

2ኛው ከተማ አቀፍ የአዲስ አበባ የፖሊስ ስፖርት ውድድር ቅዳሜ ይጀምራል

መጋቢት 3 ቀን 2018 ዓ/ም ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶቸ እና ስፖርት ቢሮ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት 2ኛው ከተማ አቀፍ የፖሊስ ስፖርት ውድድር ተልዕኮን በጀግነነት ስፖርትን በውጤት በሚል መሪ ቃል መካሄድ ይጀምራል፡፡

ውድድሩን አስመልከቶ ዛሬ በአዲስ አበባ ፖሊሰ መመሪያ በተሰጠወ ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ከመጋቢት 5 እስከ 19 2018 ዓ/ም በሚቆየው ስፖርታዊ ውድድርና ፌስቲቫል ላይ በስድስት ስፖርት አይነት 13 ቡድኖች የተውጣቱ ከ1ሺ 800 በላይ ስፖርተኞች እንደሚሳፉ ተመልከቷል

የፖሊስ አባላቱ በስፖርታዊ ውድድሮች መሳተፋቸው አብሮነት እና ወንድማማችነትን እንደሚያተናክር የገለጹት የአዲስ አበባ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳዊት ትርፉ ውድድሩ ሕዝባዊ ግዴታቸውን በንቃትና በጥሩ ስነ-ምግባር ለመወጣት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርላቸው ገልጸዋል።

የመክፈቻው ዝግጅት በአበበ ቢቅላ ስቴድየም ስካሄድ ሌሎች ውድድሮች በተመረጡ የስፖርት ማዘውተርያ እና ስፖርት ማዕከላት እንደሚካሄድ ያመላከቱት አቶ ዳዊት ከተማችን ሞዴል የተሞክሮ ማዕከል የሚያደርግ ስፖርታዊ ውድድር መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የፖሊስ አበላት ለከተማዋ ሰላምና ልማት እየተወጡ ካሉት ዘርፈ ብዙ ስራ ባሻገር በስፖርታዊ ውድድር መሳተፋቸው የታነጸ ስብዕና እንዲኖራቸው ያስችላል ያሉት የአዲስ አበባ ፖሊስ መመሪያ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በውድድሩ አገራችን የሚስጠሩ ስፖርተኞች እንደሚገኙበት አመላክተዋል፡፡

የከተማዋ ስፖርት ወዳድ ማህበረሰብ በሜዳው በመገኘት ለጸጥታ ሃይሉ ያለውን አጋርነት እንዲያሳይ ጥሪ ያቀረቡት ኮማንደሩ ውድድሩ በፖሊስ ሥነ ምግባር እና በስፖርታዊ ጨዋነት እንደሚካሄድ አሳውቀዋል፡፡

በውድድሩ ላይ 11ም ክፍለ ከተሞች የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መመሪያ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሌጅ የሚሳፉ ሲሆን በአትሌቲክስ፣ እግር ኳስ፣ ጠረጴዛ ቴኒስ፣ ዳርት፣ ቮሊቦል እና ገመድ ጉተታ ብርቱ ፉክክር እንደሚካሄድ ተመልክቷል፡፡

 

"

 

"

  • icon 9:30am - 1:00pm
  • አዲስ አበባ, Abebe Bikala Stadium

Related Events

image description
ስፖርት

  • አዲስ አበባ, Abebe Bikala Stadium
More Details